ባለስልጣናት ምስክርነት እንዳይሰጡ ፍ/ቤት ወሰነ
ሐሙስ፣ ጥር 3 2010ማስታወቂያ
የመንግስት ባለስልጣናት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ በቀለ ገርባ እና ሌሎች በነ ጉርሜሳ አያኖ መዝገብ በፀረ/ሽብር ሕግ በተከሰሱት ችሎት ላይ ለመከላከያ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ የተከሳሶች ጠበቃ ያቀረቡትን ጥያቄ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬው ውሎው «በሙሉ ድምፅ» ውድቅ አድርጎታል። ውሳኔው እንደተሰማ ተከሳሾች ተቃውሟቸውን የትግል መዝሙር በመዘመር በማሰማታቸው ፍርድ ቤት ደፍራችኋላ በሚል በተከሳሾች ላይ ከሶስት ወር እስከ ስድስት ወር የእስራት ቅጣት እንደተላለፈባቸው እና ለጥር 10 ቀን 2010 ዓ ም ተለዋጭ ቀጠሮ እንደተሰጠ በፍርድ ቤቱ ተግኝቶ የነበረዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር የላከው ዘገባ ያመለክታል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር
ልደት አበበ