ባህላዊ፣ የፍቅር ዜማ
ሐሙስ፣ መጋቢት 4 2000ማስታወቂያ
ዘፈን፣ የሰዉ ልጅ በኑሮዉ ዉስጥ ያለበትን ችግር ለመፍታት የሚጠቀምበት ዘዴ ነዉ ሲሉ ምሁራን ይገልጻሉ። በአገራችን በተለይ በገጠሩ አካባቢ የስልጣኔዉን አለም እንብዛም የማያዉቀዉ፣ ዘፈንን በአዕምሮዉ ጠይቆ ሊመልሳቸዉ ያልቻላቸዉን ነገሮች በማንጎራጎር በዘፈን ፍች ሊሰጥባቸዉ ይሞክራል። ለምሳሌ የጨለማ የቀን መፈራረቅ የተራራ መብዛት፣ በቅሎ የሴት ተፈጥሮ ኖርዋት አለመዉለድዋ የመሳሰሉት ጥያቄዎችን መልስ ለመስጠት ይገጥማል አስፈሪ የሆነ ነግርም ካለ በንጉርጉሮ፣ በዜማ እንደሚወጣ ጽሁፎች ይገልጻሉ። የህብረተሰብ ጥናት አዋቂዉ አቶ መስፍን መሰለ ስለፍቅር ዘፈኖች ያጫዉቱናል መልካም ቆይታ።