ባህላዊ መጠሪያዎችና ፍቻቸዉ
ቅዳሜ፣ ሐምሌ 18 2001ማስታወቂያ
ወደ መሃል አገር ወደ ሸዋ አካባቢ በአብዛኛዉ የጀግንነት ሁኔታን የሚገልጹ ስሞችን እናገኛለን። ለምሳሌ ደባልቄ፣ ለጥይበሉ የመሳሰሉ ስሞችን። ሌላዉ ሰያሚዉ የደረሰበት ታሪክ ለማዉሳትም ለስምነት ይጠቅምበታል። ለምሳሌ አቶ ተክሉ በወጣትነት እድሚያቸዉ ትምህርት እንዳጠናቀቁ በድንገት በበጋ ወቅት ሴት ልጅ ቢወልዱ፣ በበጋ ወር እሸት አይለቀምም፣ እኔ ግን በበጋ ወቅት ያገኘሁሽ እሸቴ ነሽ ሲሉ ልጃቸዉን የበጋእሸት ተክሉ ብለዉ ሰይመዋታል።
የታዋቂዉ ኢትዮጽያዊ ደራሲ የበአሉ ግርማ አብሮ አደግ ጓደኛ አቶ ታደሰ ደግሞ የጓደኛቸዉ የአቶ በአሉ ግርማ በድንገት መሰወር ልባቸዉ ቢነካ ወንድ ልጅ ሲወልዱ ለደራሲዉ ማስታወሻ ብለዉ ልጃቸዉን ከአድማስ ባሻገር ታደሰ ብለዉታል። ስለ አገራችን ባህላዊ እና ዘመናዊ የስም አወጣጥ በአዲስ አበባ ዪንቨርስቲ በቋንቋዎች ጥናት ማዕከል የስነ-ልሳን መምህር ከአቶ ሙሉሰዉ አስራቴ ጋር ቆይታ አድርገናል ያድምጡ
የታዋቂዉ ኢትዮጽያዊ ደራሲ የበአሉ ግርማ አብሮ አደግ ጓደኛ አቶ ታደሰ ደግሞ የጓደኛቸዉ የአቶ በአሉ ግርማ በድንገት መሰወር ልባቸዉ ቢነካ ወንድ ልጅ ሲወልዱ ለደራሲዉ ማስታወሻ ብለዉ ልጃቸዉን ከአድማስ ባሻገር ታደሰ ብለዉታል። ስለ አገራችን ባህላዊ እና ዘመናዊ የስም አወጣጥ በአዲስ አበባ ዪንቨርስቲ በቋንቋዎች ጥናት ማዕከል የስነ-ልሳን መምህር ከአቶ ሙሉሰዉ አስራቴ ጋር ቆይታ አድርገናል ያድምጡ