በግብፅ ባለስልጣናቱ እገዳ ተጣለባቸው
ቅዳሜ፣ የካቲት 5 2003ማስታወቂያ
ባለስልጣናቱ መጓዝ ከፈለጉም ከጦሩ ፍቃድ ማግኘት እንዳለባቸው ተጠቁሟል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞው የግብፅ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ የት እንዳሉ በውል ለማወቅ አልተቻለም። አንዳንዶች ሻርም አል ሼክ ወደተሰኘችው ሌላኛዋ የግብፅ ከተማ ተዛውረዋል ሲሉ ይደመጣሉ። የአረብ ብዙኋን መገናኛ ደግሞ ሙባረክ ከሀገር ወጥተው ወደ አውሮፓ፣ አለያም ከባህረ-ሰላጤው ሀገራት ወደ አንዱ ሳያቀኑ አልቀሩም ይላሉ።
ማንተጋፍቶት ስለሺ