በዓለማችን የተስፋፋው የሞት ቅጣት
ዓርብ፣ መጋቢት 19 2006ማስታወቂያ
በጎርጎሮሳውያኑ 2013 ዓም በዓለማችን በሞት የተቀጡ ሰዎች ቁጥር ከቀዳሚዉ ዓመት 2012 ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እንደነበረ ተዘገበ ። ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል ትናንት ባወጣው ዘገባ በ2013 በሞት የተቀጡ ሰዎች ቁጥር በ15 በመቶ ጨምሯል ። ለዚህም ድርጅቱ በምክንያትነት ያቀረበው በዓመቱ ኢራን፤ በኢራቅና ሳውዲ አረቢያ በሞት የቀጧቸዉ ሰዎች ቁጥር ማደጉ ነው ። ድርጅቱ እንደሚለው በዚሁ ዓመት በዓለማችን በአጠቃላይ 778 ሰዎች በሞት ተቀጥተዋል ። በድርጅቱ መግለጫ መሠረት በይፋ ከተፈፀሙ ከእነዚህ ቅጣቶች በተጨማሪ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቻይና በድብቅ በሞት ተቀጥተዋል ። የዶቼቬለው Michael Gessat የዘገበውን ይልማ ኃይለ ሚካኤል አጠናቅሮታል ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሂሩት መለሰ
ነጋሽ መሀመድ