በውቅያኖስ ውሃ፣ ምድረ-በዳን፣ ምድረ-ገነት ማድረግ፣
ረቡዕ፣ ሰኔ 17 2001ማስታወቂያ
ታዲያ፣ አንድ እንግሊዛዊ ተመራማሪ፣ የአትክልት ችግኝ ማፍያ የመስታውት ቤቶችን፣ ከውቅያኖስ በቧንቧ በሚጠለፍ ውሃ፣ ልምላሜ-በልምላሜ እንዲሆኑ ማብቃታቸው፣ ምድረ -በዳ ቀመስ ለሆኑ አገሮች ሠናይ ዜናም ሆነ ብሥራት ሳይሆን አልቀረም። ተጣርቶ የሚቀርበው የውቅያኖስም ሆነ ጨው የበዛበት ውሃ የሚሰጠው ጠቀሜታ ተደራራቢ መሆኑ የሚታበል አይደለም።
መርኀ-ግብሩና አሠራሩ ቀላል ነው። ፀሐይ፣ ውቅያኖስን ታሞቃለች። የባህሩ ውሃ፣ እየተነነ ወደ አየር ይወጣና በዚያ ከቀዘቀዘ በኋላ፣ ርዶ ደመና ይፈጥራል። በኋላም፣ ዝናም ሆኖ ሲውርድ የጨውነት ጣዕም አይኖረውም። የብሪታንያው ተወላጅ ቻርሊ ፓተን፣ በዚሁ የተፈጥሮ ህግ አካሄድ ረገድ ነው የመስታውት ቤቶችን የሚያስጌጡት። ፎልከር ማርሴክ በዚህ ዙሪያ አጠር ያለ ጽሑፍ አቅርቧል። ተክሌ የኋላ አጠናቅሮታል።
ተክሌ የኋላ፣
ሒሩት መለሰ፣