1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኤርትራ ባለሥልጣናት ላይ የቀረበው ጥቆማ ውድቅ መደረጉ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 10 2006

አቃቤ ህግ ፣ህጉ ሥራ ላይ እንዲውል ከተደረገበት እለት በኋላ የተፈፀሙ ወንጀሎችን ብቻ የሚመለከት መሆኑን ሰሞኑን በማሳወቅ ጥቆማውን ውድቅ አድርጓል ።

https://p.dw.com/p/1Cef0
ምስል AP

የስዊድን አቃቤ ህግ ፣የስዊድን የህግ ባለሞያዎች በስብዕና ላይ ወንጀል ፈፅመዋል ሲሉ የኤርትራውያን ባለሥልጣናትን ስም ዝርዝር ያቀረቡበትን ጥቆማ ውድቅ አደረገ ። የህግ ባለሞያዎቹ በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀመ ወንጅል በስዊድን ህግ የሚያስጠይቅ እንዲሆን በተፈቀደበት በጎርጎሮሳውያኑ ሐምሌ 1 2014 ዓም የኤርትራው ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ና ሶስት ሚኒስትሮችን እንዲሁም አማካሪያቸው በሰብዕና ላይ ወንጀል ፈፅመዋል ሲሉ ስማቸውን ጠቁመው ነበር ። ይሁንና አቃቤ ህግ ፣ህጉ ሥራ ላይ እንዲውል ከተደረገበት እለት በኋላ የተፈፀሙ ወንጀሎችን ብቻ የሚመለከት መሆኑን ሰሞኑን በማሳወቅ ጥቆማውን ውድቅ አድርጓል ።የስቶክሆልሙ ዘጋቢያችን ቴዎeሮስ ምህረቱ ዝርዝሩን ልኮልናል ።

ቴዎድሮስ ምህረቱ

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ