1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኢንጋቢሬ ላይ የተላለፈው ብይን

ረቡዕ፣ ጥቅምት 21 2005

የርዋንዳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተቃዋሚው የተባበሩት ዴሞክራሲያዊ ኃይላት ኢንኪንጊ መሪ ወይዘሮ ቪክቷር ኢንጋቢሬ ላይ ትናንት የስምንት ዓመት እሥራት በየነ። ፍርድ ቤቱ ኢንጋቢሬን የሀገራቸውን መንግሥት በሽብር ተግባር ለመጉዳት አሢረዋል።

https://p.dw.com/p/16aHI
Rwandan opposition leader Victoire Ingabire wears handcuffs, as she listens to the judge during the her trial in Kigali, Rwanda Monday, Sept. 5, 2011. Ingabire, an outspoken critic of President Paul Kagamea's regime, is charged with allegations of providing financial support to a terrorist group, causing state security and formenting ethnic divisions. (Foto:Shant Fabricatorian/AP/dapd)
ቪክቷር ኢንጋቢሬምስል dapd

እአአ በ1994 ዓም የተካሄደውን የጎሣ ጭፍጨፋ ክደዋል በሚል በተመሠረቱባቸው ሁለት ክሶች ጥፋተኛ ሆነው አግኝቶዋቸዋል።
በርዋንዳ የተቃዋሚው የተባበሩት ዴሞክራሲያዊ ኃይላት ኢንኪንጊ መሪ ወይዘሮ ቪክቷር ኢንጋቢሬን የመጨረሻ ብይን ለማስማት የመጣው ሰው ፍርድ ቤቱን አጣቦ ነበር። በእሥር ላይ የሚገኙት ኢንጋቢሬ ስድስት የተለያዩ ክሶች ቢመሠረቱባቸውም፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽዋን በሁለቱ፡ ማለትም፡ ርዋንዳን በሽብር ተግባር ለመጉዳት አሢረዋል፡ እንዲሁም፡ እአአ ከ1994 ዓም በብዛት የቱትሲ ጎሳ የተገደሉበትን የጎሳ ጭፍጨፋ ክደዋል በተሰኙት ክሶች ጥፋተኛ ሆነው እንዳገኛቸው አስታውቋል።

ቀደም ሲል በተጠቀሱት ሕግጋት መሠረት፡ በዚህ ዓይነቱ ክስ ፍርድ ፊት ሲቀርቡ ይህ የመጀመሪያ ጊዚያቸው በመሆኑና፡ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በሽብር ተግባር ለመጉዳት ማሤራቸው ከባድ ተፅዕኖ ባለማሳረፉ፡ ቅጣታቸው ተቀንሶዋል። በሁለት ክሶች ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ስምንት ዓመት እሥራት ተበይኖባቸዋል።
ኢንጋቢሬ በሌሎች አራት ክሶች፡ አንድ የአሸባሪዎች ድርጅት ለማቋቋም እና የሀገሪቱን ሥነ ሥርዓት የሚያውኩ ጭምጭምታዎች ለመንዛት አሢረዋል በተባሉባቸው ክሶች ጭምር ጥፋተኛ እንዳልሆኑ ዳኛው አስታውቀዋል። ብይኑን በተሰጠበት ጊዜ ኢንጋቢሬ በፍርድ ቤቱ አልተገኙም፤ ኢንጋቢሬ በርዋንዳ የፍትሕ አውታር ላይ እምነት እንደሌላቸው በመግለፅ ካለፈው ሚያዝያ ወር ወዲህ ጉዳያቸውን ከተመለከተው ችሎት ርቀዋል።
ብይኑን እንደማይቀበሉት ያስታወቁት የኢንጋቢሬ ጠበቃ ያን ኤድዋርድስ በብይኑ አንፃር የሚወስዱትን ርምጃ እንዲህ ሲሉ ገልጸዋል።
« ቀጣዩ ርምጃችን ይግባኝ ማለት ነው። ዛሬ በተላለፈው ብይን አንፃር የይግባኝ ማመልከቻ እናስገባለን። በተቻለ ፍጥነት ወደ ላዕላዩ ፍርድ ቤት እንሄዳለን። »
ልክ እንደ ኢንጋቢሬ ጠበቃ ብዙዎቹ በፍርድ ቤት ችሎቱን የተከታተሉት የኢንጋቢሬ ፓርቲ ደጋፊዎች በብይኑ መገረማቸውን ገልጸዋል። የተቃዋሚው የተባበሩት ዴሞክራሲያዊ ኃይላት ኢንኪንጊ መሪ ኢንጋቢሬ ምክትል ቦኒፋስ ቱዋጊሪማና ፍርድ ቤቱ ያስተላለፈው የስምንት ዓመት እሥራት ቅጣት በፍፁም ትክክል እንዳልሆነ አመልክተዋል።
« በጣም ነው የተገረምነው። መሪያችን መፈታት ነበረባቸው። ምንም ዓይነት ስህተት አልሰሩምና። ጥፋተኛ አይደሉም። »
በኢንጋቢሬ ላይ እአአ ከ1994 ዓም የጎሣ ጭፍጨፋ ጋ በተያያዘ ለተመሠረተባቸው ክስ መነሻ የሆነው ኢንጋቢሬ እአአ ጥር፡ 2010 ዓም በርዋንዳ በተካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ለመወዳደር በስደት ከነበሩባት ኔዘርላንድስ ወደ ሀገራቸው በተመለሱበትና በመዲናይቱ ኪጋሊ የሚገኘውን እአአ ለ1994 ዓም የጎሣ ጭፍጨፋ የተሰራውን መታሰቢያ በጎበኙበት ጊዜ የሰጡት አስተያየት ነበር። ኢንጋቢሬ በጎሣ ጭፍጨፋው ወቅት ለተገደሉት ለዘብተኛ የሁቱ ጎሣ አባላት ሞት ተጠያቂዎቹ ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ሲሉ ተናግረው እንደነበር ይታወሳል።
በኢንጋቢሬ ችሎት ወቅት ዓቃብያነ ሕግ የኢንጋቢሬን በሽብር ተግባር ተሳትፎ ያሳያል ያሉዋቸውን ማስረጃዎች፡ እንዲሁም፣ ኤፍ ዲ ኤል አር ኤ ለተባለው እና በጎረቤት ዴሞክራቲክ ኮንጎ ለሚገኘው የሁቱ ዓማፂ ቡድን ገንዘብ አስተላልፈዋል ያሉበትን ማስረጃ ጭምር አቅርበዋል። ፍርድ ቤቱ የኤፍ ዲ ኤል አር ኤ አባል መሆናቸውን ባመኑ እና በርዋንዳ ላይ ጥቃት የሚሰነዝር አንድ ቡድን እንዲያቋቁሙ ከኢንጋቢሬ ገንዘብ እንደተቀበሉ በመሰከሩ ሌሎች አራት ተከሳሾች ላይ ከሁለት እስከ አራት ዓመት እሥራት በይኖዋል።

GettyImages 154345045 Rwanda's jailed opposition figure, Victoire Ingabire [R] leaves the Supreme court on October 18, 2012 in the capital Kigali. Rwanda's Supreme Court on Thursday rejected a suit filed by a leading opposition figure challenging one of the laws being used to prosecute her for allegedly denying the 1994 genocide. Victoire Ingabire, who has been in custody for two years accused of bankrolling terrorism as well as denying the genocide, filed a suit in March contesting the legality of Rwanda's genocide ideology laws. AFP PHOTO / Stephanie AGLIETTI (Photo credit should read STEPHANIE AGLIETTI/AFP/Getty Images)
ምስል AFP/Getty Images
Es geht um ruandische und ugandische Verwicklungen bei einer Rebellion im Nordkivu. --- 2012_10_18_nordkivu.psd
Rwandan opposition leader Victoire Ingabire , left, listens to her British defence counsel Iain Edwards, during her trial in Kigali, Rwanda Monday, Sept. 5 2011. Ingabire, an outspoken critic of President Paul Kagamea's regime, is charged with allegations of providing financial support to a terrorist group, causing state security and formenting ethnic divisions. (Foto:Shant Fabricatorian/AP/dapd)
ኢንጋቢሬ ከጠበቃዋ ኤድዋርድስ ጋምስል dapd

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ