1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአቶ ዮናታን ክስ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 28 2008

ችሎቱ አቶ ዮናታን የተከሰሱባቸው ጽሁፎች ፣የመናገር ነጻነት ላይ የተደረጉ ክልከላዎችን እና የፀረ ሽብሩን አዋጅ 652 /2001 አንቀጽ 4 ን የሚተላለፉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ብሏል ።

https://p.dw.com/p/1JbiV
Symbolbild Justiz Richter Gericht Richterhammer
ምስል picture-alliance/dpa/U. Deck

[No title]


ዛሬ ያስቻለው የኢትዮጵያ ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19 ነኛ ወንጀል ችሎት የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዮ በተከሰሱበት የፀረ ሽብር ህግ እንዲከላከሉ ብይን ሰጠ ። ችሎቱ አቶ ዮናታን የተከሰሱባቸው ጽሁፎች ፣የመናገር ነጻነት ላይ የተደረጉ ክልከላዎችን እና የፀረ ሽብሩን አዋጅ 652 /2001 አንቀጽ 4 ን የሚተላለፉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ብሏል ። ፍርድ ቤቱ አቶ ዮናታን የመከላከያ ምስክሮች ይዘው እንዲቀርቡ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ። ችሎቱን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝሩን ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ