1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በትምህርት ላይ የመከረው የአዲስ አበባ ስብሰባ 

ሐሙስ፣ መስከረም 25 2010

በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጠው ትምህርት ተጥራት ችግር አለበት ተባለ። በትምህርት አገልግሎት ውስጥ ያሉ ባለድርሻዎች የጥራት ባህል የላቸውም ሲሉ ዶ/ር አበባው ይርጋ  ተችተዋል።

https://p.dw.com/p/2lIcC
Äthiopien Goethe-Institut Konferenz
ምስል DW/Y. Gebireegziabher

ውይይት በትህርት ጥራት ላይ

ዶ/ር አበባው ይርጋ  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳይሬክተር ናቸው። ዶ/ር አበባው የከፍተኛ ትምህርት አገልግሎት በኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ገንዘብ ቢመደብለትም የተፈለገውን የጥራት ደረጃ ማምጣት አልተቻለም ሲሉ ተችተዋል። ትችቱ የተደመጠው በጀርመን የተማሩ ባለሙያዎች እና የመንግሥት ባለሥልጣናት በመከሩበት ስብሰባ ላይ ነው። ስብሰባውን የተከታተለው ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር የሚከተለውን ዘገባ አድርሶናል። 
ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር
እሸቴ በቀለ
ነጋሽ መሐመድ