በስዑዲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይዞታ
ዓርብ፣ ታኅሣሥ 18 2006ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ተወላጆች ፤ በሰላም እጃቸውን ለፖሊስ እንዲሰጡ በተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ማቅረባቸው ተነግሯል።መጀመሪያ ሥራ ካሠጣቸው ተያዥ ጋር ግንኙነት የሌላቸው እንደ ሕገ ወጥ ሠራተኞች እንደሚታዩ የስዑዲ መንግሥት አስታውቋል ተብሏል። በዚህ ሁኔታ ቁጥራቸው ከ 80 ሺ እስከ 100ሺ የሚገመት ኢትዮጵያውያን ፣ ሕገ-ወጥ ተብለው አገር እንዲለቁ ሊገደዱ ይችላሉ ቢባልም ፣ አብዛኞቹ ፣ ከተያዥዎቻቸው እውቅና ውጭ ሥራ አግኝተው እየሠሩ የሚኖሩ እንዲባረሩ የሚያደርግ እርምጃ ይወሰዳል ብለው እንደማይገምቱ ነው የሚነገረው። ይሁንና ፣ በሚመጡት ቀናት ሊወሰድ የሚችለው እርምጃ እጅግ አሳሳቢ ሊሆን እንደሚችል ግምት አለ። በዚህ ጉዳይ ላይ ነቢዩ ሲራክ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሮ ልኮልናል።
ነቢዩ ሲራክ
ተክሌ የኋላ
ኂሩት መለሰ