1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በስኬትቦርድ ከአዲስ አበባ እስከ ሀረር ጉዞ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 18 2005

ካሳለፍነው ማክሰኞ ጀምረው ሰባት ኢትዮጵያዊ እና የውጭ ዜግነት ያላቸው ወጣቶች ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ሀረር ጎዞ ጀምረዋል። ጉዞዋቸው በመኪና ወይንም በብስክሌት አይደለም፤ በስኬትቦርድ ነው። ስለዚህ ረዥም ጉዞ እና የስኬት ቦርድ አነዳድ የዛሬው የወጣቶች አለም ትኩረት ይሆናል።

https://p.dw.com/p/18NRc
epa03413483 Skateboarder Manny Santiago from the USA kick-flips his board during a practice session of the 2012 Skateboarding World Championships Maloof Money Cup in Kimberley, South Africa, 28 September 2012. The world's best skateboarders are competing for the biggest cash prize in skateboarding in the three disciplines of street, vert and mega ramp. EPA/NIC BOTHMA
ምስል picture-alliance/dpa

ትንሽ ነው ከጠፍጣፋ እንጨት የተሰራ፣አራት ጎማዎች ያሉት ምናልባትም መካከለኛ መክተፊያ ያክላል። ሰሞኑን ፤ አዲስ አበባን ከሀረር ከሚያገናኘው ጎዳና ላይ እንደዚህ አይነት እንጨት ላይ ቆመው ወይንም በአንድ እግራቸው እየገፉና ጣውላው ላይ ዘለው እየቆሙ የሚጓዙ ወጣቶች አይታችሁ ከሆነ ፤ የስኬትቦርድ ነጂዎች ናቸው። ካሳለፍነው ማክሰኞ ጀምረው ከአዲስ አበባ -ሀረር ጉዞ ጀምረዋል። ትናንት አዋሽ ደርሰው ዕረፍት ሲያደርጉ ከጉዞ ተካፋዮቹ መካከል ሁለቱን በስልክ አነጋግረናቸዋል።

An Australian skate trainer trains the Afghan children in Kabul, Afghanistan.09.09.2012.Photo :(Skateistan) Afghan children are playing with skate in Kabul, Afghanistan.09.09.2012.Photo :(Skateistan) Skateistan gives permission to Deutsche-Welle to use these pictures (included in the link and the photos of Oliver sent previously).
ምስል Skateistan

የ 16 አመቱ አቤነዘር ከሁለት አመት በፊት ነው እስኬትቦርድ መንዳት የተማረው። ዛሬ የዚህ ጉዞ ተካፋይ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ስኬትቦርድ የምንነዳ ከሰላሳ በላይ እንሆናለን ይላል አቤነዘር። ይህን ብዙም ያልተለመደ የአነዳድ ዘዴ በሰሞኑ ጉዞዋቸው ለሌሎች ለማስተዋወቅ መንገድ ከፍቶላቸዋል።

በዚህ ጉዞ ከአቤነዘር ሌላ 6 የስኬትቦርድ ነጂዎች አሉ። ሚካኤል ፋሲል ግን ዛሬ ምድቡ በቪዲዮና ፎቶ ማንሳት ስራ ላይ ነው። ሚካኤል በዚህ ጉዞው የቪዲዮ ዘገባውን ሲያሰናዳ እንደው የሰዉን አመለካከት እንዴት እንዳገኘው ገልፆልናል።

ከ500 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት በሰው ሀይል በሚንቀሳቀስ ስኬትቦርድ መንዳት መቼም ብዙ ጉልበት መጠየቁ አይቀሬ ነው። ትንሽ ብያደክምም መንገድ ላይ የምናያቸው ደስ የሚሉ ነገሮች ይበልጥ ቀጥለን እንድነዳ ያበረታቱናል ይላል አቤነዘር። ምባልባት ነገ አልያም እሁድ ተጓዦቹ እና አብሮዋቸው ያሉት አጃቢዎች ሀረር እንደሚደርሱ ተስፋ ያደርጋሉ።

እስካሁን ስለነበራቸው ጉዞ ማወቅ ከፈለጋችሁ የድምፅ ዘገባውን ይጫኑ።

ልደት አበበ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ