በርሊንና የዉድ ተሽከርካሪዎች መጋየት
ረቡዕ፣ ነሐሴ 11 2003ማስታወቂያ
ትናንት ምሽት ከተፈጸመዉ ሌላ ቀደም ባለዉ ቀንም እንዲሁ 18 መኪኖች በተመሳሳይ መንገድ መንደዳቸዉ ተገልጿል። ድርጊቱ የተፈጸመዉ በሃብታሞች መኖሪያ አካባቢ መሆኑን ያመለከተዉ የፖሊስ መረጃ ወንጀሉ የተፈጸመዉ ምናልባት በናጠጡ ሃብታሞችና ተቋሞች ላይ ተቃሞዉ ያላቸዉ የግራ ጽንፈኞች ያደረጉት ሊሆን እንደሚችል ግምቱን ሰንዝሯል። ምናልባትም ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ አፍላ ታዳጊ ወጣቶች ድርጊትም ሊሆን እንደሚችልም ተገምቷል። የአዉቶሞቢል ቃጠሎዉ የትናንት እና ከትናንት በስተያ ብቻ እንዳልሆነ ነዉ የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል የሚያስረዳዉ።
ይልማ ኃይለሚካኤል
ሸዋዬ ለገሠ
ተክሌ የኋላ