በሞያሌው ግጭት የባለስልጣናቱ እጅ
ሰኞ፣ ሐምሌ 23 2004ማስታወቂያ
በግጭቱ 18 ሰዎች መገደላቸው እና በሺዎች የሚቆጠሩት ወሰን አቋርጠው ወደ ኬንያ እንደሸሹ ተዘግቧል። እንደ በርካታ የዜና አውታሮች ገለፃ ከኬንያ ድንበር 1 ነጥብ 6 ኪሎሜትሮች ርቀት ላይ በምትገኘው ሞያሌ ተቀስቅሶ የነበረው ግጭት ጋሪ እና ቦረና በተሰኙት ሁለት ጎሳዎች የመሬት ባለቤትነት ውዝግብ ሳቢያ ነበር የተነሳው።
የተለያዩ የዜና አውታሮች በግጭቱ 18 ሰዎች ተገድለው 12 መቁሰላቸውን እንዲሁም በሺዎች የሚቆጠሩት መሰደዳቸውን መዘገባቸው ይታወቃል። በሁለቱ ጎሳዎች መካከል የተነሳው የመሬት የይገባኛል ጥያቄ አዲስ ሳይሆን ቆየት ያለ እንደሆነ ነው የሚነገረው። እንዲያም ሆኖ ግን የጎሳ አባላቱ ለረዥም ጊዜያት ጥይት ሲያከማቹ እና መሳሪያ ሲሰበስቡ ያስቆማቸው ሀይል አልነበረም ይላሉ የአካባቢው ነዋሪ።
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ተክሌ የኋላ