በምሥራቅ ኢትዮጵያ የተከሰተዉ የምግብ እጥረት
ዓርብ፣ መስከረም 9 2001ማስታወቂያ
በምሥራቅ ኢትዮጵያ በሶማሌ መስተዳድር የተከሰተዉ የምግብና የዉሐ እጥረት አሳሳቢ ደረጃ ለይ መድረሱን የተባበሩት መንግሥታት የሠብአዊ ርዳታ ማስተባባሪያ ቢሮ (OCHA) በድጋሚ አስታወቀ።ቢሮዉ እንደሚለዉ ችግሩ በርካታ ሕዝብን ከገጠር ወደ ከተማ እያሰደደ ነዉ።በአካባቢዉ የሚደረገዉ ወታደራዊ ዘመቻም ለችግሩ መባባስ አንድ ምክንያት ሆኗል።በኢትዮጵያ የOcha ተጠሪና የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጪ ግንባር ቃል አቀባይ ሥለ ኦጋዴን ሁኔታ የሚሉት የተለያ ነዉ።ነጋሽ መሐመድ አጠናቅሮታል።