በሊብያ ያሉ ኤርትራውያን ስደተኞች የገጠማቸው ችግር
ማክሰኞ፣ ሐምሌ 6 2002ማስታወቂያ
ድርጅቶቹ እንዳስረዱት፡ የሊብያ የጸጥታ ኃይላት ሁለት መቶ የሚሆኑ ኤርትራውያን ስደተኞችን ሚስራታህ ከሚባለው የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ በግዳጅ በረሃማ ወደሆነው ወደ ብራክ መጠለያ ጣቢያ አዛውረዋቸዋል። ስደተኞቹ በዚያ እንግልት ስለደረሰባቸውም አስቸኳይ ርዳታ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። ወደ ኤርትራ ቢመለሱ የመታሰር እና የመሰቃየት ዕጣ ሊገጥማቸው ስለሚችል፡ የሊብያ መንግስት ስደተኞቹን በግዳጅ ወደ ሀገራቸው እንዳይመልስ የአውሮጳ ህብረት የሚቻለውን እንዲያደርግ ድርጅቶቹ በተጨማሪ ጠይቀዋል።
ገበያው ንጉሴ
አርያም ተክሌ
ተክሌ የኋላ