ሶማልያና የአንዲት ጀርመን እንደራሴ አስተያየት4 ሚያዝያ 1999ሐሙስ፣ ሚያዝያ 4 1999ካለፉት ጥቂት ቀናት ወዲህ መዲናዋ ሞቃዲሾ ብርቱ ሁከት በሚታይባት ሶማልያ መረጋጋት ለማውረድ ይቻል ዘንድ ዓለም አቀፍ ጥረት ቀጥሎዋል። በዚሁ ጥረት መደዳ በተለይ በወቅቱ የአውሮጳ ኅብረትን የፕሬዚደንትነት ሥልጣን የያዘችው ጀርመን ትልቅ ሚና ልትጫወት እንደሚገባት በጀርመን ፌዴራዊ ምክር ቤት ቡንድስታክ የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ እንደራሴ ዶክተር ኡሺ አይት ለዶይቸ ቬለ ባልደረባ ሉድገር ሻዶምስኪ በሰጡት ቃል ምልልስ አስረድተዋል። የእንደራሴዋን ቃለ ምልልስhttps://p.dw.com/p/E0YXየአረንጓዴዎቹ ፓርቲ እንደራሴ ኡሺ አይትምስል PA/dpaማስታወቂያ ይዘት አርያም ተክሌ እንደሚከተለው አሰባስባዋለች።