1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስፖርት ፤ ታህሳስ 4 ቀን፣ 2008 ዓ.ም

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 5 2008

በፈረንሳይ በሚደረገዉ አገር አቋራጭ አትሌቲክስ ዉድድር የጀርመን አትሌቲክስ ቡድን በአራት አጠቃላይ ሜዳሊያ ሦስተኛ ደረጃን ይዞአል።

https://p.dw.com/p/1HNDJ
Fußball Bundesliga Borussia Dortmund - Eintracht Frankfurt
ምስል Getty Images/Bongarts/L. Baron

በፈረንሳይ በተካሂደው የ 2015 የአውሮጳ አገር አቆዋራጭ የአትሌቲክስ ውድድር የእንግሊዝ አትሌቲክስ ቡድን በአገኘው አጠቃላይ 9 ሚዳልያ ቀዳሚ ሲሆን የስፔን አትሌቲክስ ቡድን በ 6 ሜዳልያዎች ሁለትኛ የጀርመን አትሌቲክስ ቡድን ደግሞ 4 ሚዳልያ በማግኘት ሶስትኛ ደረጃን ይዞአል።

በእንግሊዝ የባርክ ሌይ ፕርሚየር ሌግ አስራ ስድስተኛ ሳምንት የእግር ኳዋስ ጨዋታ አሁንም ለትንበያ አስቸጋሪ መሆኑን ቀጥልዋል ቅዳሚ ትንሹ ቦርንማውዝ ግዙፉ ማንችስተር ዮናይትድን ሁለት ለአንድ አሸንፎዋል። ክርስታል ፓላ ሳውዝ ሀምፕተንን፣ ዋትፈርድ ሰንደርላንድን አንድለ ባዶ በሆነ ተመሳሰይ ውጤት ሲያሸንፉ፣ ማንችስተር ሲቲ ስዋንዚን ሁለት ለአንድ ረትዋል እሁድ አርሰናል አስቶቪለን ሁለት ለበዶ ረትዋል ማክሰኞ ታጅሳስ 5 ሌስተር ሲቲ ከቸልሲ የጫወታል።

Fußball Bundesliga Bayer 04 Leverkusen vs. Borussia Mönchengladbach
ምስል Getty Images/Bongarts/S. Steinbach

የእንግሊዝን ፕርሜየር ሊግ አርሰናል ለጊዚው በ 33 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ሲመራው አንድ ተስተካካው ጨዋታ የሚቀረው ሌስትር ሲቲና ማንችስተር ሲቲ 32 ነጥብ ሁለትኛ እና ሶስተኛ ሆነው ይከተለሉ። ማንችስተር ዩናይትድ 29 ነጥ 4 ደረጃ ላይ የገኛል። ኖርዊች ሰንደርለንድ እና አስቶንቬላ 18 19 20 ኛ ላይ ናቸው ።

በጀርመን ቡንዲስሊጋ

አጉስበርግ ሻልካን ሁለት ለዜሮ ዶርቱ መንድ ፍራንክፈርትን አራት ለአንድ ረተዋል ባየር ሙኒክ ኢንጉሽታድን ሁለት ለዜሮ አሸንፎዋል። በጀርመን ቡንዲስ ሊጋ ባየር ሙኒክ በ 43 ነጥብ ሲመራ ቦሬስያ ዶርቱ መንድ በ 38 ነጥብ ሁለተኛ ሆኖ ይከተላል። ሃርታ በርሌን በ 29 ነጥብ ሶስታኛ ሲሆን ቮልፍስበርግ 26 ነጥብ ይዞ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። ሀኖቨር ሆፍንሀም እና ሽቱትጋርት በወራጅ ቀጠና የተቀመጡ ናቸው።

ሀና ደምሴ

አዜብ ታደሰ