ስደተኞችና የጦር ሐይል ዘመቻ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 22 2007ማስታወቂያ
ሜድትራኒያን ባሕር ላይ ከስምንት መቶ በላይ ስደተኞች ካለቁ ወዲሕ ዳግም እልቂትን ለመከላከል የሠሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት አባል መንግሥታት የባሕር ጦራቸዉን ወደ ሜድትራኒያን ባሕር እያዘመቱ ነዉ።የጦር ተሻራኪዉ ድርጅት አባል የሆነችዉ ጀርመን ሕንድ ዉቅያኖስ፤ ቀይ ባሕር እና ፋርስ ባሕረ-ሠላጤ አካባቢ ከሚገኙ መርከቦችዋ የተወሰኑትን ወደ ሜድትራኒያን ባሕር አዝምታለች።የባሕር ሐይሉ ተልዕኮ ስደተኞችን ማዳን ብቻ ሳይሆን ስደተኛ አሸጋጋሪዎችንም አድኖ መያዝ ነዉ።የዘመቻዉን ዓላማና ዉጤት በተመለከተ የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ይልማ ሐይለ ሚካኤልን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ይልማ ኋለ ሚካኤል
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ