1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስዊድን በጉዲፈቻ ያደጉ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን

ሰኞ፣ ሚያዝያ 6 2006

ስዊድን በጉዲፈቻ ያደጉ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ማህበር ባለፈው እሁድ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ባዘጋጀው ስብሰባ የማህበሩ አባላትና ሃገር ቤት የሚገኙ ወላጆቻቸው እርዳታና ምክር በሚያገኙበት መንገድ እንዲሁም በጉዲፈቻ ማዕከል ምሥረታ ላይ ተነጋግረዋል ።

https://p.dw.com/p/1Bhrs
Blick auf Stockholm
ምስል dpa

በጉደፈቻ ስዊድን ተወስደው ያደጉ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያንና በሚያጋጥሟቸው ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ላይ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መከሩ ። ስዊድን በጉዲፈቻ ያደጉ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ማህበር ባለፈው እሁድ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ባዘጋጀው ስብሰባ የማህበሩ አባላትና ሃገር ቤት የሚገኙ ወላጆቻቸው እርዳታና ምክር በሚያገኙበት መንገድ እንዲሁም በጉዲፈቻ ማዕከል ምሥረታ ላይ ተነጋግረዋል ። በዚሁ ስብሰባ ላይ የተገኙት በስዊድን የኢትዮጵያ አምባሳደር የማህበሩን አባላት ችግሮች ለመፍታት ኢትዮጵያና ስዊድን የሚገኙ ጉዳዩ የሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች በትብብር መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል ። ስብሰባውን የተከታተለው የስቶክሆልሙ ዘጋቢያችን ቴዎድሮስ ምህረቱ ዘገባ አለው ።

ቴዎድሮስ ምህረቱ

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ