1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ሳሪስ የሷሊህ መስጊድ ኢማም ግድያ

ዓርብ፣ ሰኔ 10 2003

በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሳሪስ አቦ በሚባለዉ አካባቢ የሚገኘዉ የሷሊህ መስጊድ ኢማም ሼኽ መሐመድ አደም፤

https://p.dw.com/p/RUKG

ማክሰኞ ሰኔ ሰባት ለረቡዕ አጥቢያ ከንጋቱ አስር ሰዓት ከአርባ አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች በቤታቸዉ ደጃፍ ይህወታቸዉ አልፏል። የኢማም ሼኽ መሐመድ ግድያ በአንድ በኩል ፖለቲካዊ ይዘት እንዳለዉ በሌላ በኩል ደግሞ በግል ጸብ የሚፈልጓቸዉ ሰዎች እጅ እንደተፈፀመ የሚገልፁ ጥቆማዎች ለዶቼ ቬለ ደርሰዋል። ፖሊስ በበኩሉ የወንጀሉን ተጠርጣሪዎች ይዞ ምርመራዉን በከፍተኛ ደረጃ እያጣራ እንደሚገኝ ተገልጿል። ዶቼ ቬለ የደረሰዉን ጥቆማ መሠረት በማድረግ የአዲስ አበባዉ ወኪላን ታደሰ እንግዳዉ የሚከተለዉን ዘገባ በጉዳዩ ላይ አጠናቅሯል።

ታደሰ እንግዳዉ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ