1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ምርጫ በህንድ

ዓርብ፣ ሚያዝያ 9 2001

በህንድ ምርጫ እየተካሄደ ነዉ። ሰባት መቶ አስር ሚሊዮን መምረዝ የሚችል ህዝብ ግን አደባባይ ወጥቶ በአንድ ቀን መሪዎቹን መምረጥ አልቻለም፤ በጸጥታ ስጋት ምክንያት።

https://p.dw.com/p/HZFg
ድምፅ ለመስጠት በሰልፍ ላይ
ድምፅ ለመስጠት በሰልፍ ላይምስል AP

እናም በአምስት ደረጃ ምርጫዉ እንደሚካሄድ ይፋ ሆኗል። በዓለም ላይ ትልቋ የዴሞክራሲ አገር በምትባለዉ ህንድ ታዲያ የምርጫ ሂደቱ አንድ ወር ይፈጃል ተብሏል። ትናንት የመጀመሪያዉ ደረጃ አልፏል። ሆኖም ግጭትና ጉዳት ደርሷል፤ ሰዎች ሞተዋል፤ ፖሊሶችም ቆስለዋል። ከደፈረሰዉ ጸጥታ ጀርባ የማኦ ተከታዮችና አክራሪ ሙስሊሞች እንዲሁም ተስፈንጣሪ ቡድኖች እንዳሉበት በብዙዎች ዘንድ ተገምቷል።

ይልማ ኃይለሚካኤል/ሸዋዬ ለገሠ