1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ማየት የተሳነው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ በሶማሊላንድ

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 1 2003

ማየት የተሳነው የ26 ዓመት ወጣት ስደተኛ ነው። ገና ዕውቅና ባላገኘችው ግን ራሷን ሐገር ብላ በሰየመችው ጎረቤት ሶማሊላንድ ውስጥ በስደት ሲባትት አራት ዓመታትን አስቆጥሯል። ታዲያ ተስፋ ያጣች መንፈሱን ዘወትር በብዕሩ ጠብታ በሚያፈልቃቸው የግጥም ሰንኞቹ ለማፅናናት ይሞክራል። በስደት ዓለም መከራ፦ ከአብራኩ የተከፈሉት ሁለቱ ብላቴናዎቹ

https://p.dw.com/p/RGJv
ማየት የተሳናቸው የብሬል መፃፊያ
ማየት የተሳናቸው የብሬል መፃፊያምስል picture-alliance/ ZB
እንዲያ አብረውት የመጎሳቆላቸው ዕጣ ልቡን ሲያደማው ደግሞ፤ ለራሱ በሚያንጎራጉረው ዜማ ውስጡን ለማከም ይሞክራል። ከምንም በላይ ግን አድማጭ አጥተው በስደት አብረውት የሚንከራተቱ ግጥሞቹን የሚያደምጥለት ያገኘ ለት መንፈሱ ሠላም አግኝታ እንደምትረጋ ይገልፃል። ወጣቱን በስደት የሚኖርበት ሶማሊላንድ ደውዬ አነጋግሬዋለሁ። ግጥሞቹንም፣ የመሰደዱ ሰበብንም ያስደምጠናል። ለዝግጅቱ ማንተጋፍቶት ስለሺ ነኝ ፤አብራችሁን ቆዩ። ማንተጋፍቶት ስለሺ ሂሩት መለሰ