« ማሬ ኖስትሩም» እና የባህር ላይ ስደተኞች እጣ ፋንታ
ማክሰኞ፣ መስከረም 27 2007ማስታወቂያ
ኢጣልያ ከዚያን ጊዜ አንስቶ በባህር ኃይሏ ባቋቋመችው « ማሬ ኖስትሩም» በተባለው ግብረ ኃይል አማካኝነት የመስመጥ አደጋ ያሰጋቸውን ስደተኞች የማዳን ሥራ እያከናወነች ትገኛለች። ግብረ ኃይሉ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ 91 ሺ በላይ ሰዎችን ህይወት ማትረፍ ቢችልም ከ 3000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች አሁንም ባህር ላይ ህይወታቸዉን አጥተዋል። ይኼው የሟቾች ቁጥር ግብረ ኃይሉ በታቀደው መሠረት በቅርቡ ሥራውን የሚያጠናቅቅ ከሆነ በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል የሚል ስጋት አለ። በየቀኑ ወደ አውሮፓ ስለሚጓዙት ስደተኞች እጣ ፋንታ እና ማሬ ኖስትሩም ቀጣይ ይዞታ የብራስልስ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።
ገበያው ንጉሴ
ልደት አበበ
ሸዋዬ ለገሰ