1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

መኢአድ፡ መድረክ እና ሰበር ሰሚ ችሎት

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 13 2002

ምርጫ 2002 ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው ፍትሃዊ አልነበረም፡ ምርጫውም መደገም አለበት በማለት ይህንኑ ጥያቄአቸውን ያስረዳል ያሉትን ዝርዝር ክስ እና ማስረጃ ቀደም ሲል ለምርጫ ቦርድ እና ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አቅርበው ነበር።

https://p.dw.com/p/OQ52
ምስል DW

ይሁንና፡ ሁለቱ አካላት ክሱንና ማስረጃዎቹን ሳይመለከቱ ውድቅ በማድረጋቸው፡ ይኸው አሰራራቸው ህገ መንግስቱን እና የምርጫ ህጉን ሙሉ በሙሉ የጣሰ በመሆኑ የህጉን ጥሰት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሰበር ሰሚ ችሎት ተመልክቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት መኢአድ እና መድረክ ክስ መሰርተው ነበር። የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሰበር ሰሚ ችሎትም ጉዳዩን ተመልክቶ ዛሬ ባሳለፈው የመጨረሻ ብይን የቀረበው ማስረጃ ምርጫውን ሊያስደግም አይችልም በሚል ክሱን ውድቅ አድርጎታል።

ታደሰ እንግዳው

አርያም ተክሌ
ሸዋዬ ለገሰ