1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ላይፕሲሽ ለተገን ጠያቂዎች ያወጣችው እቅድ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 11 2004

በላያፕዚሽ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ተገን ጠያቂዎች እስከዛሬ በነበረው አሰራር ከህብረተሰቡ ተገልለው በተወሰነ አካባቢ እንዲቆዩ ነው የሚደረገው ። ወደፊት ግን ከህብረተሰቡ ጋር ተሰባጥረው በከተማይቱ በሞላ በተለያዩ ቤቶች እንዲኖሩ ለማድረግ ታስቧል ።

https://p.dw.com/p/15ZyK
Ein Zaun und eine Videokamera sichern das Asylbewerberheim am Samstag (30.06.2012) in der Torgauer Straße in Leipzig. Das Heim in einer ehemaligen Russenkaserne muss wegen des schlechten Standards in nächster Zeit geschlossen werden, die Asylbewerber sollen in Mietshäusern quer über die Stadt verteilt wohnen. Seit dieses Konzept der Stadt vorliegt, gibt es Bürgerproteste. Foto: Jan Woitas dpa/lsn
ምስል picture-alliance/dpa

በላያፕዚሽ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ተገን ጠያቂዎች እስከዛሬ በነበረው አሰራር ከህብረተሰቡ ተገልለው በተወሰነ አካባቢ እንዲቆዩ ነው የሚደረገው ። ወደፊት ግን ከህብረተሰቡ ጋር ተሰባጥረው በከተማይቱ በሞላ በተለያዩ ቤቶች እንዲኖሩ ለማድረግ ታስቧል ። ይህ ሃሳብም የውጭ ዜጎች ከህብርተሰቡ ጋር ተዋህደው የሚኖሩበትን ሁኔታ በሚያጠኑ ባለሞያዎች ዘንድ ተወድሷል ። ይሁንና ህብረተሰቡ ሲቃወመው ነው የሰነበተው ። ተቃውሞውም በከፊል ዘረኝነት የሚንፀባረቅበት ነበር ። በዚህ ሐሳብ ላይ ብዙ ውይይቶችና ማሻሻያዎች ከተደረጉበት በኋላ የከተማይቱ ምክር ቤት ዛሬ ሐሳቡን ያፀድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል ። አድርያን ክሪሽ ያቀረበውን ዘገባ ሂሩት መለሰ አጠናቅራዋለች ።

ላይፕዚሽ ከጀርመን መዲና በርሊን በሰተደቡብ 200 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው የምትገኝ ከተማ ናት ። የከተማይቱ ከንቲባ ቶማስ ፋብያን ተገን ጠያቂዎች በላይፕዚሽ ህብረተሰቡ መካከል እንዲኖሩ ያቀረቡትን አዲስ ሃሳብ ለማስረዳት ከሁለት ወራት በላይ በከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች ተዘዋውረዋል ። የከተማው አስተዳደር  በከተማይቱ ደቡብ ምስራቅ  በሚገኘው በሪቤክሽትራሰ ሰፈር ለ 115 ተገን ጠያቂዎች ቤት ለመከራየት አስቧል ። የአካባቢው ነዋሪዎች ግን ስጋት አላቸው ።

Ein Schild "Anmeldung für Besucher" hängt am Samstag (30.06.2012) am Eingang zum Asylbewerberheim in der Torgauer Straße in Leipzig. Das Heim in einer ehemaligen Russenkaserne muss wegen des schlechten Standards in nächster Zeit geschlossen werden, die Asylbewerber sollen in Mietshäusern quer über die Stadt verteilt wohnen. Seit dieses Konzept der Stadt vorliegt, gibt es Bürgerproteste. Foto: Jan Woitas dpa/lsn
ምስል picture-alliance/dpa

«አብዛኛዎቹ የራይበቤክ ሽትራሰ ነዋሪዎች በዚህ ህንፃ ዙሪያ በእግር ይንሸራሸራሉ ።   አዛውንቶች ወጣት ወንዶች በበቡድን ተሰብስበው ቆመው  ሲያዩ መፍራታቸው አይቀርም »

« የትኛዋ እናት ናት ህፃን ልጇን ይዛ በማታ በፈቃደኝነት ወደ እኔ የድንገተኛ ህክምና ክሊኒክ የምትመጣው ? »

« በህንፃችን ውስጥ የሚገኙት የስነ ልቦና ችግሮችም ሆነ የጥርስ ሃኪሞቹ ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው ገልፀውልናል ። ቤቱን ለቀው ለመውጣት እያሰቡም ነው ። »

ነዋሪዎች እነዚህን መሰል ስጋታቸውን ሲገልፁ ከንቲባ ቶማስ ፋብያን ደግሞ ለ670 ተገን ጠያቂዎች አዳዲስ መኖሪያዎችን ማግኘት አለባቸው ። ርሳቸው ባፈለቁት በዚህ ሃሳብ ብዙ አበረታች አስተያየቶችን አግኝተዋል ። ሃሳቡን የተቃወሙዋቸውም ጥቂት አይደሉም ። ሆኖም ፋቢያን ስጋት ያደረባቸው ነዋሪዎች ሃሳባቸውን መቀየራቸው እንደማይቀር ነው ተስፋ የሚያደርጉት ።

« ባለፉት ሳምንታት በተለያዩ ቦታዎች ስለ ውጭ ዜጎችና ስለ ስደተኞች ይነሱ የነበሩት በጣም ጥሩ ያልሆኑ አስተያየቶች ነክተውኛል ። አንዳንዶቹ አስተያየቶች በጣም የተጋነኑና ደስ የማያሰኙ ነበሩ ። በዚያው ልክ ደግሞ ብዙ የተለሳለሱና እኛንም በእጅጉ የሚያበረታቱም ነበሩ ። በኔ ግንዛቤ ይህ በግልፅ የብዙሃኑ አመለካከት ነው ።»

Der somalische Asylbewerber Sahardid Jama-Ahmed. Copyright: DW/Adrian Kriesch Juli, 2012, Leipzig
ዛሃርዲድ ጃማ አህመድምስል DW

በላይፕዚሽ ከተማ ለተገን ጠያቂዎቹ ወደፊት ስለታሰበው መኖሪያ በሚካሄደው ክርክር ውስጥ የመነጋገሪያ ርዕስ የሆኑት ሰዎች አልተካተቱም ። ከነዚህም አንዱ ሶማሊያዊው ዛሃርዲድ ጃማ አህመድ ነው ። ከዛሬ 10 ዓመት አንስቶ 200 ተገን ጠያቂዎች በሚገኙበት በቶርጋወር ሽትራሰ ነው የሚኖረው ። ወንደ ላጤዎች በበዛት የሚገኙበትን ይህን ባለ ድርብ አጥርና ያልታደሰ ስፍራ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ለሰው መኖሪያ አይሆንም ሲል  ሊዘጋው አቅዷል ። በዚህ መጠለያ የሚኖረው ዛርዲድ ጀርመንኛ አቀላጥፎ ይናገራል ።

« በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ የሚፈፀምብኝን እድልዎ ለምጄዋለሁ ።ሆኖም ሰዎች ከተዋወቁኝ በኋላ ብዙዎቹ ሙሉ በሙሉ ይቀየራሉ ፤ አዎ ሁሌም እንደሚባለው ሰው ካላወቀህ በመጠኑም ቢሆን መጠንቀቁ አይቀርም ።»

የ40 ዓመቱ ዛርዲድ ለብቻው የሚኖርበት ቤት ማግኘት ይፈልጋል ። አሁን ባለበት አነስተኛ ክፍል ብዙ ዝንቦችና በረሮዎች አሉ ። ለዛርዲድ ከህብረተሰቡ ጋር ተዋህዶ የመኖሩ እቅድ ትልቅ ችግር ነው ። ተገን ጠያቂዎች አንድ ቁርጥ ውሳኔ ስላላገኙ ከህብረተሰቡ ጋር እንዲዋሃዱ የሚሰጣቸው አግልግሎት ዝቅተኛ ነው ። ለምሳሌ ዛርዲድ የአጥንት ህክምና ባለሞያ ነው ። ሆኖም እንዲሰራ አይፈቀድለትም ፤ በየሶስት ወሩ በሚራዘም ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ነው ያለው ።  አሁን በላይፕዚሽ የተጀመረው ጥረት ችግሮቹን በሙሉ ባያቃልልም ከ 100 ነዋሪዎች 6 ቱ ብቻ የውጭ ዜጋ በሆነባት በዚህች ከተማ ተገን ጠያቂዎች ከህብረተሰቡ ጋር ተዋህደው እንዲኖሩ ለማድረግ አንድ ጠቃሚ እርምጃ መሆኑ ይታመናል ።

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ