1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለመቅዲሾ ራድዮ ጣብያ ስርጭት መቀጠል፣ የአሜሪካ ተሳትፎ

ረቡዕ፣ ሰኔ 6 1999

በሶማልያ ለ 4 ቀናት ታግደዉ የቆዩት ሶስት የግል ራድዮ ጣብያዎች ስራቸዉን ጀመሩ። ባለፈዉ ሳምንት ስርጭታቸዉን እንዲያቆሙ የታዘዙት፣ ሸበሌ ራድዮ፣ ራድዮ ሆርን አፍሪክ እና የቁራን ድምጽ፣ የተሰኙት ራድዮ ጣብያዎች ፣ ጸጥታን ያዛባሉ ፣ ከአመጸኞች ጋር ግንኙነት አላቸዉ በሚል ነበር የስርጭት እገዳ የተጣለባቸዉ

https://p.dw.com/p/E0YJ

ለነዚህ ራድዮ ጣብያዎች እንደገና መከፈት የዩናይትድ ስቴትስ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ትልቅ ሚናን እንደተጫወተ ተገልጾአል። በሌላ በኩል በያዝነዉ ሳምንት ሶማልያ ከጣልያን ቅኝ ግዛት እንደተላቀቀች የሶማልያ ፕሪዝደንት ሆነዉ ያገለገሉት Aadan Abdulle Osman ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። Aadan Abdulle Osman ለበርካታ አመታት በጣና ታመዉ በኬንያ የህክምናቸዉን በመከታተል ላይ ነበሩ። በዚህ ጉዳይ ዙርያ በመቅዲሾ የሚገኘዉን የሸበሌ ራድዮ ጋዜጠኛ አዊስ ኦስማን ዩሱፍን አዜብ ታደሰ በስልክ አናጋግራዉ ነበር